Professor Takele Tadesse

ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ

ዋና ዳይሬክተር

አግኙን

የፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ

እንኳን ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት አቅም ግንባታና ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በደህና መጡ። ይህ የኢንስቲትዩት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የተቋማት አቅምን ለማሳደግ፣ በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ አቀራረብን ለማጠናከር እና የክልሉን ዘላቂ ልማት ለመደገፍ በቁርጠኝነት ይሰራል።
የኢንስቲትዩታችን በ2023 ዓ.ም በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ የአቅም ግንባታ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ የፖሊሲ ጥናቶችን በማካሄድ ግንባር ቀደም የልቀት ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህንን እውን ለማድረግ ኢንስቲትዩቱ በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ጥናቶችን በማካሄድ ተፅዕኖ ፈጣሪ የፖሊሲ ምክረ ሀሳቦች በማቅረብ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ጥራት ያላቸው የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመንደፍና በመስጠት የተቋማት ብቃት በማጠናከር፣ ተግባራዊ እና ውጤት ተኮር የምክር አገልግሎት በመስጠት፣ የፖሊሲ ተፈጻሚነትን በማሻሻል ውስጣዊ የአሰራር ስርዓት፣ ሰው ኃይል እና መረጃ አስተዳደር ልህቀትን በማጠናከር፣ ከአጋሮች ጋር በተቀናጀ ሁኔታ ሀብት ማበልጸግና ተፅዕኖ በማሳደግ የክልሉን መንግስት ያግዛል።
በፈጣን ለውጦች በሚኖሩበት ዘመን ውጤታማ አስተዳደር የጠንካራ ትንተና አቅም፣ የተሻለ የሰው ሀይል እና ጠንካራ የተባባሪነት ግንኙነት ይጠይቃል። በመሆኑም ኢንስቲትዩታችን ከክልል ቢሮዎች፣ ከአካዳሚያዊ ተቋማት፣ ከልማት አጋሮች እና ከማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ፖሊሲዎች አካታች፣ ተገቢ እና ለህዝቡ ፍላጎት የሚመሩ እንዲሆኑ ይሰራል። በአቅም ግንባታ ስልጠና፣ በፖሊሲ ጥናቶች እና በተቋማት አቅም ግንባታ ላይ መዋዕለ ንዋይ ማድረግ ጠንካራና የተሻለ ወደፊት ያለው ክልል ለመገንባት አስፈላጊ መሆኑን እናምናለን። በአመራር ብቃት ማጠናከር፣ የአስተዳደር ስርዓቶችን ማሻሻል እና በህዝብ አገልግሎት ውስጥ ፈጠራን ማበረታታት በኩል ለተሻለ አስተዳደር እና ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንሰራለን።
በጋራ በአቅም ግንባታና ፖሊሲ ጥናት ላይ በመስራት ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ የተሻለ ወደፊት እንገንባ።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያለመታከት ተቋማትን ለማጠናከር፣ ባለሙያዎችን በአስፈላጊ ክህሎትና እውቀት ለመገንባት እና ማስረጃ ላይ የተመረኮዙ የፖሊሲ ጥናት ሥራዎችን ስንሰራ ቆይተናል፡፡ የአቅም ግንባታ ሥራዎች እንዲሁ የለሆሳስ ሥልጠናዎች መስጠት ሳይሆን ተለዋዋጭነትን የሚቋቋም፣ ፈጠራን የሚያቀላጥፍ፣ አመራርን ለልህቀት የሚያበቃ እና ባለሙያዎች ያሉትን የወቅቱ ተግዳሮቶች እንዲጋፈጡ የሚያደርጉ ተግባራት ናቸው፡፡ የፖሊሲ ጥናት ሥራዎቻችን ደግሞ የጠነከሩ ምርምሮችን እና ሁሉን አካታች ምክክሮችን መሰረት ያደረጉ ለተመራማሪዎች፣ ለተቋማትና ለድርጅቶች አቅጣጫ ተቋሚ ሆነው ማህበራዊ ፍትህንና ዘላቂ ብልጽግናን ማዕከል ያደረጉ ናቸው፡፡
ከፊታችን ያለውን ከፍ ብለን ስንመለከት መሻታችንና ተልዕኮአችን በኢንስቲትዩቱ ጥረት ብቻ የሚሳካ አይደለም፡፡ በመሆኑም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ፖሊሲ አውጪዎች፣ የአካዳሚክ ምሁራን፣ ባለሙያዎችና ዜጎች ለተቋማችን ተልዕኮ ስኬት ከእኛ ጋር እንድትተባበሩና እንድትቀናጁ የአክብሮት ጥሪ አቀርባለሁ፡፡ በጋራ ሆነን አገራችንን፣ ክልላችንንና ሕዝባችንን የሚጠቅሙ የአቅም ግንባታ ሥራዎች፣ በራስ መተማመን የሚፈጥሩና ማህበራዊ ሽግግርን የሚመጡ የፖሊሲ ጥናቶችን እና አመራር የሚኮተኩቱ ሥራዎችን እንስራ፡፡
Signature

ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ

March 08, 2026